የሃይማኖት ዕዉቀት ማስፋፊያ ማህበር yehymanote ewket masfafiya mahiber
ለቤተ ክርስቲያናችን ዛሬም ነገም በእምነትና በህብረት ሆነን እርስቷንና ስርአቷን ላናስነካ ቃል እንገባለን:: '' ቤተክርስቲያኔ ሆይ ብረሳሽ ቀኜ ትርሳኝ ባላስብሽ ምላሴ ከትናጋዬ ይጣበቅ!! ''
Tuesday 26 November 2013
Memehir G/meskel.....የ28 ዓመት መንፈሳዊ ጉዞ disc 8
http://www.youtube.com/watch?v=C3vDhDNR9qA
እግዚአብሔር ኢትዮጵያን ይባርክ !!!
Sunday 29 September 2013
የሃይማኖት ዕውቀት ማስፋፊያ ማህበር የ28ተኛ ዓመት የወንጌል የምስረታ በዓሉን በታላቅ ድምቀት አከበረ
በወርሃ መስከረም በእለተ እሁድ የቅዱስ ሚካኤል ወርሃዊ ክብረ በዓል በሚከበርበት ቀን ማለትም በ12/01/2006ዓ.ም የሃይማኖት ዕውቀት ማስፋፊያ ማህበር የ28ተኛ ዓመት የወንጌል የምስረታ በዓሉን በታላቅ ድምቀት አከበረ
በእለቱ ፕሮግራሙን በጸሎት የከፈቱት የሃይማኖት ዕውቀት ማስፋፊያ ማህበር መስራችና የበላይ ጠባቂ እንዲሁም የጠቅላላ
ጉባኤው አፈጉባኤ የሆኑት ሊቀ ትጉ.ባሕ ገ/መስቀል ኃ/መስቀል በአሉን አስመልክተው ንግግር ካደለጉ በኃላ ማህበሩ ለዚህ ደረጃ እንዲደርስ
ቀን ከለሊት ደፋ ቀና በማለት ለዚህ ላበቁት ለማህበሩ ደጋፊዎች መዕመናን ከፍ ያለ ምስጋና አቅርበዋል
በመቀጠልም በዓሉን አስመልክተው ማኅበሩ ከዛሬ ጀምሮ በሃይማኖት ዕውቀት ማስፋፊያ
ማህበር ዘተዋህዶ በሚል በEBS TV ዘወትር እሁድ ከረፋዱ
3፡30 እስከ 4፡00 ሰአት ድረስ የሚተላለፍ የቴሌቪዥን ፕሮግራም መጀመሩን ካበሰሩ በኃላ የ28ተኛ ዓመት የሚገልጽ ሻማ በመለኮስ ፕሮግራሙን በይፋ ከፍተዋል
በመጨለሻም በአባታችን በሊቀ ሊቃውንት ቆሞስ ኣባ ወልደማርቆስ ቡራኬና ቃለምዕዳን ተሰጥቶ የዕለቱ ፕሮግራም ተፈፀመ
Monday 10 September 2012
መልካም አዲስ ዓመት
በመላው ዓለም ለምትገኙ ምእመናን በሙሉ እንኳን ለ2005 ዓ.ም አዲስ ዓመት
ለዘመነ ማቴዎስ በሠላም በፍቅር አደረሳችሁ አደረሰን እያልን የከበረ ሠላምታ
እናቀርብላችኃለን፡፡
ከመንፈሳዊ ሠላምታችን በመቀጠል የምንገልፅላችሁ ነገር ቢኖር አዲሱ ዓመት
ዘመነ ማቴዎስ የሰላም ' የደስታ ' የፍቅር ' የአንድነትና የብልፅግና እንዲሆንልን
እየተመኘን ጉባኤያችን መስከረም 13 ቀን እሁድ 27ተኛውን ዓመት የምስረታ በዓሉን
በድምቀት ለማክበር በዝግጅት ላይ እንገኛለን፡፡ ሁላችሁም ይህንን በዓል ለማክበር
እንድትዘጋጁ መንፈሳዊ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን፡፡
መልካም አዲስ ዓመት
የሃይማኖት ዕውቀት ማስፋፊያ ማህበር
መሥራችና የበላይ ጠባቂ እንዲሁም
የጠቅላላ ጉባኤው ዋና ሰብሳቢ
ሊቀ ትጉ.ባሕ.ገ/መስቀል ኃ/መስቀል
እግዚአብሔር ኢትዮጵያን ይባርክ !!!
Subscribe to:
Posts (Atom)